Thursday, August 23, 2012

‹‹ አለሁ !! ›› ማለት






የሰው ህያውነት ተቋርኗዊ ግብሩ
ምንድነው ተብሎ ቢጠየቅ ተዓምሩ
መዛኝ... ምጡቅ ... ማህበራዊ
ጨቋኝ ... አጥፊ ... አድሏዊ
በሚል ይበየናል በቁም ሰውነቱ
በዛሬ ምህዋር ነገን በማስላቱ ፡፡
ግና የነገን ጆንያ የውስጡን ቋጠሮ
ማን ያውቃል ? ጭነቱን ድርጊቱን መንዝሮ ፡፡
ፊት ያለችው ጸሃይ የተምሳሌቷ ግርማ
ወበቅ ትደብቅ መብረቅ ፤ ብርሃን ትቀፍ ጨለማ
ማን ያውቃል ? የውሎዋን መዘርዝር
የርግማንዋንና ምርቃቷን ሚስጢር ፡፡
ልምድ ሆኖ ብቻ ‹‹ ፍጡሩ ›› አርበኛ
ነገን ይማርካል ‹‹ ፈጣሪ ›› ሆኖ ዳኛ
አለሁ ይላል ‹‹ ያደገው ›› እንስሳ
እንደዛሬው ሁሉ ነገንም ሳይረሳ
ግና ‹‹ አለሁ ! ›› ማለት
ታላቅ ዘበት ! የዘመኑ እብደት !!!

No comments:

Post a Comment